ገበያ አይዋሽም!
የእንቁላል ዋጋ ተወዷል። ጾም ገብቶም ዋጋው አልወረደም። ይህ ለምን ሆነ? ይህ የሆነው ለገበያው እየቀረበ ያለው የእንቁላል መጠን ከፍላጎቱ ያነሰ ስለሆነ ነው።
የእንቁላል ዋጋ ወርዶ 5 ብር የደረሰበት ጊዜ ነበር። ያኔ ብዙ የእንቁላል ዶሮ የሚያረባ ሰው ነበር። ሆኖም የመኖ ዋጋ ውድ ነበር። አርቢውም ከዛሬ ነገ ይሻላል በሚል እየከሰረ ዶሮ ማርባቱን ቀጠለ።
መኖ ለምን ተወደደ? የመኖ ዋና ግብዓቶች በቆሎና አኩሪ አተር በፀጥታ ችግር፣ ከውጭ የሚመጡ ግብዓቶች ዋጋ ደግሞ በዶላር ምንዛሪ መወደድ ምክንያት የመኖ ዋጋ ናረ። በዚህ የተነሳ ዶሮ አርቢዎቹ ከሰሩ። በኪሳራ መቀጠልም አልቻሉም። መኖ መግዣ እስኪያጡ ተቸገሩ።
የከሰሩ አርቢዎች የገና በዓልን ጠብቀው የእንቁላል ዶሮዎችን ለበዓል እርድ ሸጡ። ከዚያ በኋላ የእንቁላል እጥረት ተፈጠረ፤ ዋጋውም ቀስ እያለ ወደላይ ወጣ። ከ8 ብር ተነስቶ 9፣ 10፣ 12፣ 15፣ 17 እያለ የእንቁላል ዋጋ 20 ብር ገባ። አሁን መኖውን የሚመጥን ዋጋ ላይ ነው።
የሁዳዴ ጾም ሲገባ የእንቁላል ዋጋ ይቀንሳል ቢባልም ዋጋው አልቀነሰም። ምክንያቱም ፍላጎቱ አልቀነሰም። የረመዳን መግባትም ዋጋውን እንዳይቀንስ ያደርገዋል።
Trust the market. ገበያን እመነው። ገበያ አይዋሽም። ገበያ የሚመራው በአቅርቦትና ፍላጎት የሚዛን ጨዋታ ነው። ዋጋ የሚንረውም፣ ግርግር የሚበዛውም እጥረት ሲኖር ነው።
ገበያን እመነው!
የነዳጅ እጥረት አለ። ለዚህ ምልክቱ በየቦታው የሚታየው ሰልፍ ነው። እጥረት ከሌለ በቀር ያ ሁላ ሰልፍ አይኖርም። በቂ ነዳጅ አለ ቢባልም በየማደያው ያለው ሰልፍ አሳሳቢና እጥረት መኖሩን ጠቋሚ ነው።
በተለይ የናፍጣ እጥረት አሳሳቢ ነው። የጭነት መኪና ሲቆም የሸቀጦች አቅርቦት ይዳከማል፣ ዋጋቸውም ይንራል። ነገሩ ተያያዥ ነው። ችግሩን ለመፍታት ግን ውስብስብ አይደለም።
እንዲህ እጥረት ሲኖር የነዳጅ ዋጋ በኩንትሮባንድ ይሀን በቀጥታ ዋጋው ይጨምራል። መንግስትም የዋጋ ጭማሪ ያደርጋል።
እያለ እያለ የወር ወጪህ ይንራል።
የኢኮኖሚው ብልሃት ገና አልተገኘም።
እንደ ህዝብ ብዛታችን በአስደንጋጭ ፍጥነት ወደ ላይ እየተተኮሰ ነው። አሁን ከ130 ሚሊየን በላይ ሆነናል። ከዓለም ሀገራት ጋር ሲነጻጸር ቀድሞ ከነበርንበት 12ኛ ደረጄ ጃፓንና ሜክሲኮን ቀድመን 10ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠናል። ኢኮኖሚያችን ግን 100ኛ ደረጃ ላይም የለም።
የህዝብ ቁጥር ሲያድግ ፍላጎት ይጨምራል። ምግብ ልብስ መጠለያ፣ መድሃኒት፣ ነዳጅ፣... ፍላጎታቸው ይጨምራል። በዚያው ልክ አቅርቦት ካልጨመረ በስተቀር የፍላጎት ናዳው ችግር ውስጥ ይከተናል።
መፍትሔው አንድና አንድ ነው። አቅርቦትን መጨመር!
አቅርቦት ለመጨመር ምርትን ማብዛት ነው። ለዚህ መፍትሔው ታክስ ቀንሶ አምራች ኢንቨስተርን መሳብ፣ ሠራተኛን ማሰልጠን፣ መሬት በስፋት ማቅረብ እና የኤሌክትሪክ አቅርቦትን ማስፋት ናቸው። እነዚህ ሁሉ ግን የፖሊሲ ማሻሻያ ይፈልጋሉ።
የፖሊሲ ለውጥ በ6 ወራት ውስጥ የተጠበቀው ውጤት ካልታየ ችግር አለ።
የኢኮኖሚያችን መፍትሔ ብዙ ምርምር አይፈልግም። ያልታረሱትን መሬቶች ማረስ፣ ታክስ ቀንሶ ኢንቨስተሮችን መሳብ፣ የንግድ ስርዓቱ ላይ ያለ ቁጥጥርን መቀነስ፣ የፀጥታ ችግርን መፍትሔ መስጠት እና የመንግስት ሠራተኛን ቀንሶ አምራች ኃይል ማድረግ ናቸው።
ለምን ዙሪያ ጥምጥም እንደምንሄድ አይገባኝም።
የፕሬዚዳንት ትራምፕ አስተዳደር የአሜሪካን ኢኮኖሚ ለማነቃቃት ምን እያደረገ ነው?
ከየትም የሚገኝ ጠቃሚ ተሞክሮ ስናይ ትምህርት ወስዶ መፍትሔ ማምጣት ላይ ማተኮር አስፈላጊ ነው።
ገበያ አይዋሽም! ኑሮ ከተወደደ ችግሩ ያለው ፖሊሲው ላይ ነው።
https://t.me/+6o1ZHgKbYAA2ODc8
የእንቁላል ዋጋ ተወዷል። ጾም ገብቶም ዋጋው አልወረደም። ይህ ለምን ሆነ? ይህ የሆነው ለገበያው እየቀረበ ያለው የእንቁላል መጠን ከፍላጎቱ ያነሰ ስለሆነ ነው።
የእንቁላል ዋጋ ወርዶ 5 ብር የደረሰበት ጊዜ ነበር። ያኔ ብዙ የእንቁላል ዶሮ የሚያረባ ሰው ነበር። ሆኖም የመኖ ዋጋ ውድ ነበር። አርቢውም ከዛሬ ነገ ይሻላል በሚል እየከሰረ ዶሮ ማርባቱን ቀጠለ።
መኖ ለምን ተወደደ? የመኖ ዋና ግብዓቶች በቆሎና አኩሪ አተር በፀጥታ ችግር፣ ከውጭ የሚመጡ ግብዓቶች ዋጋ ደግሞ በዶላር ምንዛሪ መወደድ ምክንያት የመኖ ዋጋ ናረ። በዚህ የተነሳ ዶሮ አርቢዎቹ ከሰሩ። በኪሳራ መቀጠልም አልቻሉም። መኖ መግዣ እስኪያጡ ተቸገሩ።
የከሰሩ አርቢዎች የገና በዓልን ጠብቀው የእንቁላል ዶሮዎችን ለበዓል እርድ ሸጡ። ከዚያ በኋላ የእንቁላል እጥረት ተፈጠረ፤ ዋጋውም ቀስ እያለ ወደላይ ወጣ። ከ8 ብር ተነስቶ 9፣ 10፣ 12፣ 15፣ 17 እያለ የእንቁላል ዋጋ 20 ብር ገባ። አሁን መኖውን የሚመጥን ዋጋ ላይ ነው።
የሁዳዴ ጾም ሲገባ የእንቁላል ዋጋ ይቀንሳል ቢባልም ዋጋው አልቀነሰም። ምክንያቱም ፍላጎቱ አልቀነሰም። የረመዳን መግባትም ዋጋውን እንዳይቀንስ ያደርገዋል።
Trust the market. ገበያን እመነው። ገበያ አይዋሽም። ገበያ የሚመራው በአቅርቦትና ፍላጎት የሚዛን ጨዋታ ነው። ዋጋ የሚንረውም፣ ግርግር የሚበዛውም እጥረት ሲኖር ነው።
ገበያን እመነው!
የነዳጅ እጥረት አለ። ለዚህ ምልክቱ በየቦታው የሚታየው ሰልፍ ነው። እጥረት ከሌለ በቀር ያ ሁላ ሰልፍ አይኖርም። በቂ ነዳጅ አለ ቢባልም በየማደያው ያለው ሰልፍ አሳሳቢና እጥረት መኖሩን ጠቋሚ ነው።
በተለይ የናፍጣ እጥረት አሳሳቢ ነው። የጭነት መኪና ሲቆም የሸቀጦች አቅርቦት ይዳከማል፣ ዋጋቸውም ይንራል። ነገሩ ተያያዥ ነው። ችግሩን ለመፍታት ግን ውስብስብ አይደለም።
እንዲህ እጥረት ሲኖር የነዳጅ ዋጋ በኩንትሮባንድ ይሀን በቀጥታ ዋጋው ይጨምራል። መንግስትም የዋጋ ጭማሪ ያደርጋል።
እያለ እያለ የወር ወጪህ ይንራል።
የኢኮኖሚው ብልሃት ገና አልተገኘም።
እንደ ህዝብ ብዛታችን በአስደንጋጭ ፍጥነት ወደ ላይ እየተተኮሰ ነው። አሁን ከ130 ሚሊየን በላይ ሆነናል። ከዓለም ሀገራት ጋር ሲነጻጸር ቀድሞ ከነበርንበት 12ኛ ደረጄ ጃፓንና ሜክሲኮን ቀድመን 10ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠናል። ኢኮኖሚያችን ግን 100ኛ ደረጃ ላይም የለም።
የህዝብ ቁጥር ሲያድግ ፍላጎት ይጨምራል። ምግብ ልብስ መጠለያ፣ መድሃኒት፣ ነዳጅ፣... ፍላጎታቸው ይጨምራል። በዚያው ልክ አቅርቦት ካልጨመረ በስተቀር የፍላጎት ናዳው ችግር ውስጥ ይከተናል።
መፍትሔው አንድና አንድ ነው። አቅርቦትን መጨመር!
አቅርቦት ለመጨመር ምርትን ማብዛት ነው። ለዚህ መፍትሔው ታክስ ቀንሶ አምራች ኢንቨስተርን መሳብ፣ ሠራተኛን ማሰልጠን፣ መሬት በስፋት ማቅረብ እና የኤሌክትሪክ አቅርቦትን ማስፋት ናቸው። እነዚህ ሁሉ ግን የፖሊሲ ማሻሻያ ይፈልጋሉ።
የፖሊሲ ለውጥ በ6 ወራት ውስጥ የተጠበቀው ውጤት ካልታየ ችግር አለ።
የኢኮኖሚያችን መፍትሔ ብዙ ምርምር አይፈልግም። ያልታረሱትን መሬቶች ማረስ፣ ታክስ ቀንሶ ኢንቨስተሮችን መሳብ፣ የንግድ ስርዓቱ ላይ ያለ ቁጥጥርን መቀነስ፣ የፀጥታ ችግርን መፍትሔ መስጠት እና የመንግስት ሠራተኛን ቀንሶ አምራች ኃይል ማድረግ ናቸው።
ለምን ዙሪያ ጥምጥም እንደምንሄድ አይገባኝም።
የፕሬዚዳንት ትራምፕ አስተዳደር የአሜሪካን ኢኮኖሚ ለማነቃቃት ምን እያደረገ ነው?
ከየትም የሚገኝ ጠቃሚ ተሞክሮ ስናይ ትምህርት ወስዶ መፍትሔ ማምጣት ላይ ማተኮር አስፈላጊ ነው።
ገበያ አይዋሽም! ኑሮ ከተወደደ ችግሩ ያለው ፖሊሲው ላይ ነው።
https://t.me/+6o1ZHgKbYAA2ODc8
No reviews yet.